Ethiopian Missionary Fellowship
  • EMF
  • About

Sunday
​11 AM

መንፈስ ቅዱስ ይሥራ – ኢየሱስ ይታይ – እግዚአብሔር ይክበር
የቤት ቤተክርስቲያናት ሕብረት

7512 Old Keene Mill Rd
Springfield, VA 22150

discipleship 2-1-3

11/23/2023

 
Picture
For Sunday December 3 @ 11 am

የባህሪ መሰጠት 
​
እግዚአብሔር መንገዱን ያሳይሃል። 
ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥ የለም። ዓለሙም ምኞቱም ያልፋሉ፤ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ግን ለዘላለም ይኖራል። 1 ዮሐ 2፡ 15-17

የእግዚአብሔርን ፍቃድ ለማድረግ መንገዱ፦
  • ለሕይወትህ ያለውን ዓላማ በማወቅ ራዕይህ ማድረግ
  • የባህሪያትህ ክፍሎች ሁሉ ለእግዚአብሔር መሰጠት
    • ፍቃድ (ፊልጵስዩስ 2፡13)
    • አዕምሮ (ሮሜ 12፡2)
    • አካል (ሮሜ 12፡1)
    • ስሜት (ገላ 5፡19-24)
    • ሕይወት (ገላ 2፡20)
  • እግዚአብሔር ፍቃዱን እንድታደርግ የሚያደርግልህን ሁሉ በሥራ መግለጥ 
 
አዲሱ ሰው (ገላቲያ 5፡16-25)
  • በመንፈስ ተመላለሱ (keep in step with the Spirit)
  • በመንፈስ ተመሩ (led by the Spirit)
  • የመንፈስ ፍሬ (“ይኑራችሁ”) (“have” the fruit of the Spirit)
  • በመንፈስ መኖር (live by the Spirit)
 
አሮጌው ሰው (ገላቲያ 5፡16-25)
  • የሥጋ ምኞት ከመንፈስ ምኞት ተቃራኒ ነው 
  • የሥጋ ሥራ (ምኞት) የተገለጠ ነው
  • ከክፉው መሻቱና ምኞቱ ተሰቀለ

discipleship 2-1-2

11/18/2023

 
For Sunday November 26 @ 11 A.M.

ባህሪይ መሠረት 
​
እግዚአብሔርንም ለሚወዱት እንደ አሳቡም ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንዲደረግ እናውቃለን። ልጁ በብዙ ወንድሞች መካከል በኵር ይሆን ዘንድ፥ አስቀድሞ ያወቃቸው የልጁን መልክ እንዲመስሉ አስቀድሞ ደግሞ ወስኖአልና
ሮሜ ሰዎች  8:28-29
 
ልውጠት፡-
በግል፥ በሕይወት ዘመን ሁሉ፥ በመታዘዝ ግኑኝነት 
  • የክርስቶስ ባህሪይ ማንነት 
  • የመንግስቱ እሴት
  • የመልክተኛነት ተልእኮ
 
መንፈስ ቅዱስ፦ 
ስለ በጎ ፈቃዱ መፈለግንም ማድረግንም በእናንተ የሚሠራ እግዚአብሔር ነውና። ፊል 2፡13
 
ሞዴል፦
እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና። ዩሐ 5፡30

discipleship 2-1-1

11/11/2023

 
For Sunday November 19 @ 11 am

አለቃ ማነው?
​
​ፍቃዱን ማወቅና ማድረግ 
 
ስለዚሁ እኛ ደግሞ ይህን ከሰማንበት ቀን ጀምረን የፈቃዱ እውቀት መንፈሳዊ ጥበብንና አእምሮን ሁሉ እንዲሞላባችሁ እየለመንን፥ ስለ እናንተ ጸሎትን አልተውንም
ቆላ 1፡9
 
ኢየሱስም እንዲህ አላቸው፦ የእኔስ መብል የላከኝን ፈቃድ አደርግ ዘንድ ሥራውንም እፈጽም ዘንድ ነው።
ዩሐ 4፡34
 
በሰማያት ያለውን የአባቴን ፈቃድ የሚያደርግ ሁሉ፥ እርሱ ወንድሜ እኅቴም እናቴም ነውና አለ።
ማቴ 12፡50
 
የእግዚአብሔር ፈቃድ እርሱም በጎና ደስ የሚያሰኝ ፍጹምም የሆነው ነገር ምን እንደ ሆነ ፈትናችሁ ታውቁ ዘንድ በልባችሁ መታደስ ተለወጡ እንጂ ይህን ዓለም አትምሰሉ።
ሮሜ 12፡2
 
የእግዚአብሔርን ዓላማ መፈፀም
 
ብትፈቅድ ይህችን ጽዋ ከእኔ ውሰድ፤ ነገር ግን የእኔ ፈቃድ አይሁን የአንተ እንጂ እያለ ይጸልይ ነበር።
ሉቃ 22፡42
 
እኔ ከራሴ አንዳች ላደርግ አይቻለኝም፤ እንደ ሰማሁ እፈርዳለሁ ፍርዴም ቅን ነው፥ የላከኝን ፈቃድ እንጂ ፈቃዴን አልሻምና።
ዩሐ 5፡30
 
ፈቃዴን ለማድረግ አይደለም እንጂ የላከኝን ፈቃድ ለማድረግ ከሰማይ ወርጃለሁና።
ዩሐ 6፡38
 
እኔ ላደርገው የሰጠኸኝን ሥራ ፈጽሜ በምድር አከበርሁህ
ዩሐ 17፡4
    የሕሁድ ትምህርት ከሳምንት በፊት ይወጣል። ሳምንቱን ተዘጋጅተንበት እንምጣ። 
    Picture

    የአገልጋዮች ጉባኤ 

    December 2024
    September 2024
    August 2024
    July 2024
    June 2024
    May 2024
    April 2024
    March 2024
    February 2024
    January 2024
    December 2023
    November 2023
    October 2023

    Categories

    All

    RSS Feed

በፍጹምም ሕሊናቸው ፈልገውታልና፥ 
እርሱም ተገኝቶላቸዋልና 
እግዚአብሔርም በዙሪያቸው ዕረፍት ሰጣቸው።
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 15:15

በእርሱ በመታመናችሁ
የተስፋ አምላክ ደስታንና ሰላምን ሁሉ ይሙላባችሁ፤
ይኸሁም በመንፈስ ቅዱስ ሃይል
​ ተስፋ ተትረፍርፎ እንዲፈስላችሁ ነው።
​ሮሜ 15፡13 


  • EMF
  • About