Ethiopian Missionary Fellowship
  • EMF
  • About
  • USA

Sunday
​11 AM

መንፈስ ቅዱስ ይሥራ – ኢየሱስ ይታይ – እግዚአብሔር ይክበር
የቤት ቤተክርስቲያናት ሕብረት

7512 Old Keene Mill Rd
Springfield, VA 22150

May 26 - 24

4/27/2024

 
ቅዱስ ቁርባን፥ ለውይይት የቀረበ። አወያይ ፀጋዬ
ሉቃስ 22 
13 ሄደውም እንዳላቸው አገኙና ፋሲካን አሰናዱ። 
14 ሰዓቱም በደረሰ ጊዜ ከአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ጋር በማዕድ ተቀመጠ። 
15 እርሱም። ከመከራዬ በፊት ከእናንተ ጋር ይህን ፋሲካ ልበላ እጅግ እመኝ ነበር፤ 
16 እላችኋለሁና፥ በእግዚአብሔር መንግሥት እስኪፈጸም ድረስ፥ ወደ ፊት ከዚህ አልበላም አላቸው። 
17 ጽዋንም ተቀበለ አመስግኖም። ይህን እንካችሁ በመካከላችሁም ተካፈሉት፤ 
18 እላችኋለሁና፥ የእግዚአብሔር መንግሥት እስክትመጣ ድረስ ከአሁን ጀምሮ ከወይኑ ፍሬ አልጠጣም አለ። 
19 እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና። ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ። 
20 እንዲሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን አንሥቶ እንዲህ አለ። ይህ ጽዋ ስለ እናንተ በሚፈሰው በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው።

ቅዱስ ቁርባን
 
መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃዎች፡-
 ማቴዎስ 26፡26-29፣ ማርቆስ 14፡22-25፣ ሉቃስ 22፡14-20 ዮሐ 6:52-63  ሐዋ 2:42 ሐዋ 20:7,  1ኛ ቆሮንቶስ 10 : 16-17 እና በ1ኛ ቆሮንቶስ 11:17-34

መጠሪያ ስሙ ፡-
  1. ቅዱስ ቁርባን /Eucharist / thanksgiving ቅዱስ ቁርባን” ክርስቶስ ስለከፈለው ቤዛነት የምስጋናውን አካል አጉልቶ ያሳያል። የቃሉ ፍቺ ቅዱስ - ማለት የተለየ  ቁርባን "ምስጋና" ማለት ነው።
  2.  “የጌታ እራት” Lord Supper የሚለው ቃል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመጨረሻው እራት ወቅት ለተከታዮቹ የክርስቶስን ሞት መታሰቢያ የተሰጠ መሆኑን ያሳያል።
  3.  ቅዱስ ህብረት/Holy communion /  አማኞች ከክርስቶስ ጋር እና እርስ በርሳቸው  ያላቸውን ኅብረት ያጎላል። 1ኛ ዮሐ 1:3-4 ሐዋ 20:7  1ኛ ቆሮንቶስ 11:21  1ኛ ቆሮንቶስ 10 : 16-17
  4. የክርስቶስ ስጋና ደም ፦ ዮሐ 6፡ 52-63 ቃሉ ምሳሌያዊ ፍቺ ስለመሆኑ ....ቃሉ መንፈስም ሕይወትም ነው።
ቅዱስ ቁርባን ምንድነው?  ለህብረታችን / EMF /ያለው ትርጉም
  1. የክርስቶስን ሞት እና ቤዛነታችንን እንድናስታውስ የሚረዳን መታሰቢያ ነው (1ኛ ቆሮ 11፡24-25) ።
  2. ራስን የመመርመር እና የንስሐ እድል ነው (1ኛ ቆሮ 11፡27-32) ።
  3. ከክርስቶስ እና ከእርስ በርሳችን ጋር ያለን አንድነት እና ህብረት የምናደርግበት ስርአት ነው።1ኛ ቆሮንቶስ 10: 16-17፣ሐዋ. 2፡46
  4. የበረከት/የጸጋ መሳሪያ ነው። እንደ የጸጋ መሳሪያ" ክርስቲያኖች የእግዚአብሔርን ጸጋ፣ ይቅርታ እና መንፈሳዊ ምግብ እንደሚቀበሉ እና እንደሚለማመዱ የሚያሳየይ የበረከት መቀበያ ነው። 1ኛ ቆሮንቶስ 10 : 16-17
  5. ለክርስቶስ መስዋዕትነት የአምልኮ እና የምስጋና ተግባር ነው። (ሐዋ. 2፡46-47፣ ማቴዎስ 26፡26-27፣ክርስቶስ ..ባረከ...አመሰገነ.. ማርቆስ 14፡22-23፣ሉቃስ 22፡17-18
  6. የሐዲሱ ኪዳን መለያ ነው። ት.ኤር 31:31, ማቴዎስ 26፡28 1ኛ ቆሮንቶስ 11 : 25
በህብረታችን ስለመጀመር
ከላይ የተዘረዘሩት መጠሪያ ስሞች የአንዱ ስርአት መገለጫ ሲሆኑ በህብረታችን የቅዱስ ቁርባን የሚለውን በመጠቀም ስርአቱን የምናከናውን ይሆናል። በቀደመችው ቤተክርስቲያን ቅዱስ ቁርባን /የጌታ እራት/ በአማኞች ቤት ብዙ ጊዜ ይከበር ነበር (ሐዋ. 2፡46፣ 1ቆሮ 11፡20-22) ። ዛሬ በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን በተሰበሰበው ጉባኤ ላይ በብዛት ይስተዋላል። ነገር ግን፣ በአግባብና በሥርዓት እስከተከናወነ ድረስ፣ በሌሎች ተገቢ ዝግጅቶች ሊከበር ይችላል (1ኛ ቆሮ 14፡40) ።
 


Comments are closed.
    የሕሁድ ትምህርት ከሳምንት በፊት ይወጣል። ሳምንቱን ተዘጋጅተንበት እንምጣ። 
    Picture

    የአገልጋዮች ጉባኤ 

    December 2024
    September 2024
    August 2024
    July 2024
    June 2024
    May 2024
    April 2024
    March 2024
    February 2024
    January 2024
    December 2023
    November 2023
    October 2023

    Categories

    All

    RSS Feed

በፍጹምም ሕሊናቸው ፈልገውታልና፥ 
እርሱም ተገኝቶላቸዋልና 
እግዚአብሔርም በዙሪያቸው ዕረፍት ሰጣቸው።
መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 15:15

በእርሱ በመታመናችሁ
የተስፋ አምላክ ደስታንና ሰላምን ሁሉ ይሙላባችሁ፤
ይኸሁም በመንፈስ ቅዱስ ሃይል
​ ተስፋ ተትረፍርፎ እንዲፈስላችሁ ነው።
​ሮሜ 15፡13 


  • EMF
  • About
  • USA